እግዚአብሔር ቢፈቅድ የግል አቋሜ መንግሥትን በምችለው መንገድ በሃሳብ እንዲሁም በጸሎት ማገዝ እንጂ ለመንግሥት የቤት ሥራ መሆን አልፈልግም። ነገር ግን የሚታየውን ጉልህ ስህተት በግልጽ መንገር መንግሥትን ያነቃል እንጅ ጉዳት የለውም። ለሌሎችም የምመክረው ይኸንኑ ነው። ምክንያቱም ሀገር የሚመሩት ምንም መልካም ነን ቢሉ እንደ ሰው ደካማ ናቸውና ይሳሳታሉ። ስለዚህ መሪዎችን በጠላትነት ከመፈረጅ ይልቅ እንድንጸልይላቸው ታዘናል። እንኳን በከፍተኛ ኃላፊነት ውስጥ ሆነው ለሚሳሳቱት ይቅርና ለጠላቶቻችንም ልንጸልይ ይገባል። እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ '' እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤ እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።
⁴⁶ የሚወዱአችሁን ብትወዱ ምን ዋጋ አላችሁ? ቀራጮችስ ያንኑ ያደርጉ የለምን? ማቴ ፭፥፵፭