በኖህ ዘመን ለነበሩ ህዝቦች በኃጢአት ተጨማልቆ መኖር የመልካም ዘመን ውጤት እነደሆነ ቆጥረውት ነበር። እግዚአብሔር ሰውን በመፍጠሩ እስኪጸጸት ድረስ ኃጢአታቸው የበዛ ነበር። እግዚአብሔርን ለሚፈራው ኖህ ግን ክፉ ዘመን እንደነበር ዘፍ 6፥1 ስናነብ እናገኘዋለን።
የሎጥ ዘመን ዘፍ 19፥1 የእስራኤል የግብጽ ባርነት ዘጸ 1፥8 ተጽፎ እንደምገኘው በአንድ ዘመን ሁለት ዓይነት የተለያዩ ህዝቦች በተለያየ ሁኔታ ይኖሩ እንደነበር ነው። እግዚአብሔርን የሚያውቁት የተጨነቁበት እግዚአብሔር ማነው ብለው ይገዳደሩ የነበሩት በተድላና በደስታ ይኖሩ የነበረበት ዘመን ነበር። ነገር ግን የዚህ ዓለም ደስታ እንደ አይን ቅጽበት ብልጭ ብሎ የሚጠፋ በመሆኑ በቅጽበት ደስታቸው ወደ ሃዘን እንደተለወጠ እናያለን።
ወደተነሳሁበት ርእስ ስመለስ ምናልባትም ቃሉ የኛንም ዘመን የሚጠቁም በመሆኑ ለመነሻነት መረጥኩት። << ዘመኑም ክፉ ነውና ቀጥ ብላችሁ አትሄዱም። ሚክ 2፥3 >> እገምታለሁ በብዙም ባይሆን በጥቂቱ አሁን የኛን ዘመን ማን ክፉ አደረገው ? የሚል ሃሳብ ያላቸው ወገኖች ሊኖሩ ይችላሉ። ምክንያቱም የሰው ልጅ የስጋዊ ፊላጎቱ ከተሟላለት ዘመኑን በጎ አድርጎ የማየት ልምድ ስላለው ነው።
ነቢየ እግዚአብሔር ሚክያስ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ722 ዓ/ዓ አካባቢ ትንቢት ይናገር የነበረ ነቢይ ነው። ትንቢቱም ስለሰማርያና ስለ ኢየሩሳሌም መፍረስ፣ እንዲሁም እግዚአብሔር እስራኤልን እንደመንጋ እንደሚሰበስብ፣ ኢየሩሳሌም እንደገና እንደምትሰራና አህዛብም እግዚአብሔርን እሚያውቁበት ዘመን እንደሚመጣ ፣ስለጌታ በቤተልሄም መወለድም ትንቢት ተናግሯል ። ሚክ 1፥3 - 5፥1
የትንቢቱን እውነተኛነት ስንመለከት የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተልሄም ተወልዷል፣ ማቴ 2፥1፣ ለአህዛብ ምስክር ይሆን ዘንድ የእግዚአብሔር መንግስት ወንጌል በዓለም ተሰብኳል ማቴ 24፥14 ፣ ጠፍተው የነበሩት የእስራኤል ልጆች ከመላው ዓለም ተሰብስበው በማእከለ ምድር በዓለም የምትፈራ ሃገር መስርተው እየኖሩ ነው።
ወደ እኛ ስንመለስ ሃገራችን ኢትዮጵያ ከዓለም ሃገራት የተለየች ሃገር መሆኗ በብዙዎች ዘንድ የሚታወቅ ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ተጽፎ እንደምናገኘው አንድም ጊዜ ቢሆን ኢትዮጵያ እግዚአብሔርን ከማምለክ ያቋረጠችበት ዘመን እንደሌለ እንረዳለን።
ስለ ኢትዮጵያ ማንነት ከማንም በላይ ምስክሩ መጽሐፍ ቅዱስ ነው። በዚህ ታላቅና ቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ ከ40 ጊዜ በላይ ስሟ ተጠቅሶ ይገኛል። በተለይም ከዚህ በታች ያሉትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ስንመለከት ኢትዮጵያ ከእግዚአብሔር ጋር ያላትን ወዳጅነት በግልጽ እናይበታለን
ሙሴም ኢትዮጵያይቱን አግብቶአልና ባገባት በኢትዮጵያይቱ ምክንያት ማርያምና አሮን በእርሱ ላይ ተናገሩ። ዘኁል 12፥1
መኳንንት ከግብጽ ይመጣሉ ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች። መዝ 68፥31
በፊቱም ኢትዮጵያ ይሰግዳሉ፥ ጠላቶቹም አፈር ይልሳሉ መዝ 72፣9 |
አንተም የዘንዶውን ራሶች ቀጠቀጥህ ለኢትዮጵያ ሰዎችም ምግባቸውን ሰጠሃቸው። መዝ 74፥14
የኢትዮጵያ ንግድ ቁመተ ረጅሞችም የሳባ ሰዎች ወደ አንተ ያልፋሉ ለአንተም ይሆናሉ እጆቻቸውም ታስረው ይከተሉሃል በፊትህም ያልፋሉ፥ ለአንተም እየሰገዱ። በእውነት እግዚአብሔር በአንተ አለ፥ ከእርሱም ሌላ አምላክ የለም ብለው ይለምኑሃል። ኢሳ 45፥14
የኢትዮጵያ ንግድ ቁመተ ረጅሞችም የሳባ ሰዎች ወደ አንተ ያልፋሉ ለአንተም ይሆናሉ እጆቻቸውም ታስረው ይከተሉሃል በፊትህም ያልፋሉ፥ ለአንተም እየሰገዱ። በእውነት እግዚአብሔር በአንተ አለ፥ ከእርሱም ሌላ አምላክ የለም ብለው ይለምኑሃል። ኢሳ 45፥14
በውኑ ኢትዮጵያዊ መልኩን ወይስ ነብር ዝንጕርጕርነትን ይለውጥ ዘንድ ይችላልን? በዚያን ጊዜ ክፋትን የለመዳችሁ እናንተ ደግሞ በጎ ለማድረግ ትችላላችሁ። ኤር 13፣23
የእስራኤል ልጆች ሆይ፥ እናንተ ለእኔ እንደ ኢትዮጵያ ልጆች አይደላችሁምን? ይላል እግዚአብሔር፦ አሞ 9፥7 ከኢትዮጵያ ወንዞች ማዶ የሚማልዱኝ፥ የተበተኑት ሴቶች ልጆቼ፥ ቍርባኔን ያመጡልኛል። ሶፎ 3፥10
|
Amen!!! kalehiot yasemalen.
ReplyDelete