ዛሬ በሃገራችን በኢትዮጵያ እና በመላው ዓለም በሚገኙ ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ዘንድ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል የሚታሰብበት እለት ነው። የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል በዛሬው እለት ሠለስቱ ደቂቅን ( ሶስቱን ወጣቶች ) ከእሳት ያወጣበት እለት ነው። የቤተክርስቲያን አባቶች ሊቃውንት ዓመቱን በሙሉ እግዚአብሔርን እናከብር ዘንድ በተለያየ ጊዜ በቅዱሳኑ ላይ አድሮ ያደረገውን ታላላቅ ተዓምራት እናስብ ዘንድ እለታቱን በሙሉ እግዚአብሔርን እንድናመሰግንባቸው ስርዓትን ሰርተውልናል።
በሃገራችን በኢትዮጵያ በዛሬው እለት በየአብያተክርስቲያናቱ እግዚአብሔር ይመሰገናል። በተለይም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ለመታሰቢያው በተሰራለት ቤተክርስቲያን አካባቢ የሚገኙ ክርስቲያኖች ምዕመናን ከበዓሉ አስቀድመው እንግዶችን ለመቀበል ቤታቸውን ያዘጋጃሉ፣ ለእንግዶች የሚያስፈልገውን ጸበል ጸዲቅ ያዘጋጃሉ፣ እንግዶች በሚመጡበት ጊዜም እግራቸውን ያጥባሉ፣ እንግዶች ወደየመጡበት እስኪመለሱ በደስታ ተቀብለው ያስተናግዳሉ።
ይህም የሚሆንበት ምክንያት በቅዱስ መጽሐፋችን በመጽሐፍ ቅዱስ እንደተገለጸው በቃል የተነገረውን በተግባር በመፈጸም ነው።
እንግዳ ሆኜ ተቀብላችሁኛልና ማቴ 25፥35
እንግዶችን ለመቀበል ትጉ። ሮሜ 12፥13
|
እንግዶችን መቀበል አትርሱ፤ በዚህ አንዳንዶች ሳያውቁ መላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና። ዕብ 13፥1 እኛ ኢትዮጵያውያን ከመላው የዓለም ህዝብ የምንለይበት በዙ ሃይማኖታዊና ትውፊታዊ ስርዓት አለን። በዚህም የተነሳ በአሁኑ ወቅት በዓለም ብቸኛ የሆነችውን የሃይማኖት የባህልና የስርዓት ባለጸጋ የሆነችውን ሃገራችንን በተለያየ መንገድ ስሟን ለማጉደፍ ከውጭም ከውስጥም በሚነሱ ጠላቶች ተከባ ትገኛለች። በተለይ ለሃገሪቱ መታወቂያና መገለጫ የሆነችውን ቅድስት ተዋሂዶ ቤተክርስቲያንን ለማጥፋት ያልተሞከረ ነገር የለም። ነገር ግን ፈቃዱ የእግዚአብሔር ስለሆነ እስከ አሁን ደርሰናል። ለወደፊትም ይህችን የቃል ኪዳን ምድር በቅዱሳኑ ጸሎት እንደሚጠብቃት እናምናለን።
ወደ ዛሬው በዓል ስንመለስ ሁላችንም እንደምናውቀው የቅዱስ ገብርኤል በዓል ሲነሳ የቁልቢው ገብርኤል በሁላችንም አእምሮ የማይዘነጋ ነው። የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል በዚህ ቦታ ላይ ያደራጋቸውን ተዓምራት ዘርዝሮ ለመጻፍ አቅምና ጊዜ ስለማይበቃ ለመዘርዘር አይሞከርም እንዲሁ እፁብ ድንቅ ብሎ ማለፉ የተሻለ ነው።
ቅድስት ሃገር ኢትዮጵያ በነበርኩበት ጊዜ ከማገለግልባት ከደብረ አሚን ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን በየዓመቱ ታህሣስና ሐምሌ ምዕመናንን በጋራ ይዘን ከመሰል ወንድሞቼ ጋራ ወደ ቁልቢ ገብርኤል እንጓዝ ነበር። በጉዟችን ወቅት በመንገድ ላይ መንፈሳዊ ትምህርትና ዝማሬ በሰፊው ይቀርባል። እንዲሁም ከጉዞው ተሳታፊዎች በኩል መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ያደረገላቸውን ተዓምራት የሚናገሩበት ክፍለ ጊዜም ነበረን። ከሁሉ የሚደንቀው ነገር በጉዟችን ላይ የተወሰኑት የእስልምና እምነት ተከታዮች ነበሩ ። ግማሾቹ ታመው በህክምና ገንዘባቸውን ጨርሰው ተስፋ ሲቆርጡ የቅዱስ ገብርኤልን የተአምራት ዜና በመስማት ስዕለት ተስለው ከህመማቸው የተፈወሱ፣ ከፊሎቹ ልጅ መውለድ ፈልገው ወደውጭ ሃገር ድረስ ሄደው በህክምና ሞክረው አልሆን ሲላቸው በመጨረሻ ቢሆንም ባይሆንም እንሞክረው ብለው እንደቀልድ በአንደበታቸው ለቅዱስ ገብርኤል ተስለው ልጅ ያገኙ እና ሌሎችም ብዙ ለአእምሮ የሚከብዱ ጉዳዮች የተፈጸሙላቸው ይገኙበት ነበር ።
አስታውሳለሁ አቶ ጀማል የሚባሉ ሰው ልጃቸው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ውስጥ ታዋቂ እግር ኳስ ተጫዋች የሆነ (ሳዳት ጀማል)የሚባል በየዓመቱ ከጉዟችን ተሳታፊዎች አንዱ ነበሩ።
እግዚአብሔር አምላክ ለቅዱሳን መላእክት የሰጣቸውን ስልጣንና ክብር እንመልከት ።
የዚያን ጊዜም ንጉሡ ናቡከደነፆር ተደነቀ ፈጥኖም ተነሣ አማካሪዎቹንም። ሦስት ሰዎች አስረን በእሳት ውስጥ ጥለን አልነበረምን? ብሎ ተናገራቸው። እርሱም፦ ንጉሥ ሆይ፥ እውነት ነው ብለው ለንጉሡ መለሱለት።
|
እርሱም፦ እነሆ፥ እኔ የተፈቱ በእሳቱም መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ ምንም አላቈሰላቸውም የአራተኛውም መልክ የአማልክትን ልጅ ይመስላል ብሎ መለሰ።
|
የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር ወደሚነድደው ወደ እሳቱ እቶን በር ቀርቦ። እናንተ የልዑል አምላክ ባሪያዎች፥ ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም፥ ኑ ውጡ ብሎ ተናገራቸው። ሲድራቅና ሚሳቅም አብደናጎም ከእሳቱ መካከል ወጡ። ዳን 3፥24
|
በመንገድ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀሁትም ስፍራ ያገባህ ዘንድ፥ እነሆ፥ እኔ መልአክን በፊትህ እሰድዳለሁ።
|
በፊቱ ተጠንቀቁ፥ ቃሉንም አድምጡ ስሜም በእርሱ ስለ ሆነ ኃጢአት ብትሠሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት።
|
አንተ ግን ቃሉን ብትሰማ፥ ያልሁህንም ሁሉ ብታደርግ፥ ጠላቶችህን እጣላቸዋለሁ፥ የሚያስጨንቁህንም አስጨንቃቸዋለሁ።
|
መልአኬ በፊትህ ይሄዳልና፥ ወደ አሞራውያንም ወደ ኬጢያውያንም ወደ ፌርዛውያንም ወደ ከነዓናውያንም ወደ ኤዊያውያንም ወደ ኢያቡሳውያንም ያገባሃል እኔም አጠፋቸዋለሁ። ዘጸ 23፥20
ወደ እግዚአብሔርም በጮኽን ጊዜ ድምፃችንን ሰማ፥ መልአክንም ሰድዶ ከግብፅ አወጣን እነሆም፥ በምድርህ ዳርቻ ባለችው ከተማ በቃዴስ ተቀምጠናል። ዘኁል 20፥16
|
እግዚአብሔርም የበለዓምን ዓይኖች ከፈተ የእግዚአብሔርን መልአክ በመንገድ ላይ ቆሞ የተመዘዘም ሰይፍ በእጁ ይዞ አየ ሰገደም፥ በግምባሩም ወደቀ። ዘኁል 22፥31
ጌዴዎንም የእግዚአብሔር መልአክ እንደ ሆነ አየ ጌዴዎንም። አቤቱ አምላኬ ሆይ፥ ወዮልኝ የእግዚአብሔርን መልአክ ፊት ለፊት አይቻለሁና አለ። መሳፍ 6፥22
ዳዊትም ዓይኖቹን አነሣ የእግዚአብሔር መልአክ በምድርና በሰማይ መካከል ቆሞ፥ የተመዘዘም ሰይፍ በእጁ ሆኖ ወደ ኢየሩሳሌም ተዘርግቶ አየ። ዳዊትም ሽማግሌዎችም ማቅ ለብሰው በግምባራቸው ተደፉ። መ ዜና መዋ 21፥16
ሉቃ 1፥19
|
ቀሲስ እንኳን ለመልአኩ ለቅዱስ ገብርኤል በሰላም አደረሰን ቃለህይዎት ያሰማልን
ReplyDeleteKHY! E/BER yagelgelot zemenehen yabzale,yibarkele
ReplyDelete