Sunday, October 28, 2018

ሀገር አፍራሽ እንጅ ሀገር ገንቢ ስልጠና አያስፈልገውም

ይህን ጽሁፍ ከጻፍኩት ሰንበት ብሏል። ምናልባት የእኔ እይታ ሚዛናዊነት ይጎድለው ይሆን? የሚል ሃሳብ ብልቤ ይመላለስ ስለነበር ከብዙ ሰዎች ሃሳብ ለመውሰድ ሞክሬያለሁ ይሁን እንጅ ተመሳሳይ ስሜቶች ለማየት ስለቻልኩ ምናልባት ለሚመለከተውን አካል ጥቆማ መስጠቱ ከጉዳቱ ጥቅሙ ያመዝን ይሆናል በሚል ሃሳቤን ለመግለጽ ሞክሬያለሁ።

ከወር በፊት በተለያዩ ሚዲያዎች ይንጸባረቅ የነበረው ሃሳብ የብዙዎችን ቀልብ የሳበ ነበር። አህያውን ፈርቶ ዳውላውን እንዲሉ በቡድን በተደራጀ መልኩ የሰው ህይዎትና ንብረት  ሲያጠፉ የነበሩ ወገኖች ሊሰጣቸው ይገባ የነበረውን የስነ ባህርይ ትምህርት ስለ ሀገር ሰላምና አንድነት ዘብ የቆሙ የአዲስ አበባ ወጣቶችን መንግስት ሰብስቦ በማሰር ስልጠና እየሰጠሁ ነው የሚል መግለጫ ሲሰጥ ስንሰማ ይህ ነገር ከበስተጀርባው የምንፈውራ ችግር ይኖር ይሆንን? ለማለት ተገደናል? አንድ ጤነኛ የሆነ ሰውን ለህመምተኛ የሚታዘዝ መድኃኒት ቢሰጡት ከጥቅሙ ጉዳቱ የከፋ ነው። መድኃኒት የሚያስፈልገው ለበሽተኛ  ነው። ለጤነኛው ቢሰጡት በውስጡ በሽታውን ካላገኘ ሌላ የስሜት ህዋሱን ይጎዳና ለሌላ ችግር ይዳርገዋል።

በጎና ክፉ ቃላት የተናጋሪዎቹን ማንነት በጉልህ የሚያሳዩ በመሆናቸው ልንደነቅ አይገባም።

ሰዎች የሚናገሩትና የምንሰማው ሁሉ ወደ ተግባር የሚለወጥ ቢሆን በህይዎት መኖር የሚችል ፍጥረት ይኖራል ብሎ ማሰብ አይቻልም ነበር። በዓለም ላይ የተናገሩትን መፈጸም የቻሉ ሰዎች በመብራት ፈልጎ ማግኘት ከባድ ነው። በበጎም ሆነ በክፉ ሃሳብ ውስጥ ሆነው ብዙ ተናግረው ነገር ግን አንዱንም መፈጸም ያልቻሉ ብዙ ሰዎችን እናውቃለንና ምስክሮች ነን። ይህን ማድረግ የሚቻለው እግዚአብሔር ብቻ ነው። እስመ አልቦ ነገር ዘይሰአኖ ለእግዚአብሔር ሉቃ 1፥37  

የህይዎት ጉዞውን ለእግዚአብሔር መስጠት ያልቻለ ሰው ከስህተትና ከመሰናክል ሊያመልጥ አይችልም። አንዳንድ ጊዜ ከአቅም ጋር ያልተገናዘቡ ነገሮችን እሽ ብሎ መቀበል እራስን ለፈተና ማጋለጥ ነው። ብዙ ቅዱሳን አባቶቻችን ከእግዚአብሔር ያዘዘ ሹመት ስመጣላቸው ሀገር ጥለው የሸሹ እንደነበር ቅዱሳት መጻህፍት ምስክሮች ናቸው። ምክንያቱ ደግሞ እራሳቸውን ከፈተና ይጠብቁ ዘንድ ነው። እራሱን ከፍ የሚያደርግ  ሁሉ ይዋረዳል ራሱንም የሚያዋርድ ሁሉ ከፍ ይላል ማቴ 23፥ 12 - ሉቃ 14፥11

ቤተክርስቲያን በእግዚአብሔር ፈቃድ እንጅ በፕሮፓጋንዳ አትፈርስም አትሰራም።

ሰሞኑን በሶሻል ሚዲያ እየተናፈሰ ያለውን የአንድ ግለሰብ አመለካከትን የሚያንጸባርቅ ንግግር ብዙዎች ትኩረት በመስጠት ሲቀባበሉት ተመልክተናል። አቶ ጃዋር መሐመድ የሚባል የፖለቲከኝነትና የዘረንነት እንዲሁም የሃይማኖት አክራሪነትን በማንጸባረቅ የሚታወቅ ግለሰብ እንዳለ ግልጽ ነው። ይህንንም ዓላማውን በተለያዩ መድረኮች ባገኘው አጋጣሚ ሲያንጸባርቅ እንደነበር የሚያውቁት ሁሉ ምስክሮች ናቸው።  ታዲያ አሁን ምን አዲስ ነገር ተሰማና ነው ሽብር እየተነዛ ያለው? በጆሮየ ባልሰማውም ቤተክርስቲያን ይፍረስ ብሎ ተናግሯል በሚል ነው መወያያ የሆነው። ጌታ በወንጌል ‘’ከእሾህ ወይን ከኩርንችትስ በለስ ይለቀማልን ማቴ 7፥16’’ ብሎ እንደተናገረው በእኔ መረዳት ከእሱ ንግግር ይልቅ የእሱን እኩይ ዓላማ ለደጋፊዎቹ በማሰራጨት ላይ ያለነው እኛ ነን ቤተ ክርስቲያንን እየጎዳን ያለነው። በረከታቸው ይደርብንና ታላቁ የቤተክርስቲያናችን አባት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ በሁሉ ዘንድ የሚታወቅ ንግግር/ አባባል አላቸው ’’ሥራህን ሥራ” ይህ አባታዊ ምክር ብዙዎችን አንጿል። ዛሬ በየሚዲያው የቤተክርስቲያን ጠላቶች የሆኑ አካላት የሚሰነዝሩትን ቃላት ከምንሰነጥቅ ሥራችንን ብንሰራ መልካም ነው። ቤተክርስቲያን እንኳን ጃዋር የመሃመድ ልጅ መሃመድ እራሱም ቢነሳ አትሸበርም። ጃዋር ስለተናገረ ቤተክርስቲያን ይፈርሳል ብሎ የሚደነግጥ ካለ ጠባቂዋ እግዚአብሔር መሆኑን መዘንጋት ነው።
ጃዋር በጠባብ መንግድ ውስጥ ባገኘው አጋጣሚ ተልእኮውን እየፈጸመ ነው። እኛ ደግሞ እለት እለት የ