በቅዱስ ወንጌሉ እንደተጻፈው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደጋግ ተአምራት ያደረገባቸውን ምኩራባት ኮራዚ፣ ቤተሳይዳ፣ ቅፍርናሆምን ባዩት በሰሙት ነገር ባለመማራቸው እና ንስሃ ባለመግባታቸው ነቅፏቿዋል።
እነሱ በአይናቸው አይተው ያላመኑበትን ሌሎች አህዛብ ዝናውን ሰምተው እንደሚያምኑበት ያውቅ ነበርና ከሰዶምና ከገሞራ ያነሱ መሆናቸውን በምሳሌ ሲናገር ። ወንጌላዊዉ ማቴዎስ እንዲህ ብሎ ጽፏል፦
በዚያን ጊዜ የሚበዙ ተአምራት የተደረገባቸውን ከተማዎች ንስሐስላልገቡ ሊነቅፋቸው ጀመረ እንዲህም አለ፦ | |||||||||
ወዮልሽ ኮራዚ፤ ወዮልሽ ቤተ ሳይዳ፤ በእናንተ የተደረገው ተአምራትበጢሮስና በሲዶና ተደርጎ ቢሆን፥ ማቅ ለብሰው አመድም ነስንሰው ከብዙ ጊዜ በፊት ንስሐ በገቡ ነበርና። | |||||||||
ነገር ግን እላችኋለሁ፥ በፍርድ ቀን ከእናንተ ይልቅ ለጢሮስና ለሲዶና ይቀልላቸዋል። | |||||||||
አንቺም ቅፍርናሆም፥ እስከ ሰማይ ከፍ አልሽን? ወደ ሲኦል ትወርጃለሽ፤ በአንቺ የተደረገው ተአምራት በሰዶም ተደርጎ ቢሆን፥ እስከ ዛሬ በኖረች ነበርና። | |||||||||
ነገር ግን እላችኋለሁ፥ በፍርድ ቀን ከአንቺ ይልቅ ለሰዶም አገር ይቀልላታል። ማቴ 11፥20 ጌታ ይህን የተናገረው በቃሉ አስተምሮ በእጁ ተአምራት አድርጎ ነገር ግን ያንን አይተውና ሰምተው መለወጥ ላሉቻሉት ህዝቦች ነው። ከዚህ የምንማረው ዛሬ በምንሰማውና በምናየው ነገር መማርና መለወጥ ካልቻልን፣ ንስሃ ባለመግባታችን ከእግዚአብሔር ወቀሳ የማንድን መሆኑን ነው። ከጥምቀቱ ምን እንማራለን ? የሰማይና የምድሩ ንጉስ፣ ሁሉን በእጁ የያዘ፣ ከሆነው ሁሉ ያለእርሱ ፈቃድ አንዳች ነገር የሆነ የሌለ ሲሆን ነገር ግን ትህትናን ለማስተማር ነውና በሥጋ የተገለጠው በፍጡሩ እጅ ሊጠመቅ ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ ሄደ። አስቀድሞ በንስሃ መንገዱን እንዲጠርግ የተላከው መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በማቴ 3፥11 እኔ ለጠጅ ብርሌን ለልብስ ገላን እንዲያጥቡለት ለሱ ጥምቀት የሚያበቃ ጥምቀት አጠምቃችኋለሁ ለሱ ተአምኖ ኃጣውእ በሚያበቃ ተአምኖ ኃጣውእ አስተምራችኋለሁ እንጅ ክርስቶስ አይደለሁም። ከኔ በኋላ የሚመጣው እሱ ከኔ አስቀድሞ የነበረው ነው። እሱ የባሕርይ አምላክ ነው። እኔ ግን የእግሩን ጫማ ልፈታ የማይገባኝ ነኝ ። እኔ በውሃ አጠምቃችኋለሁ እሱ ግን በእሳት ያጠምቃችኋል እያለ ያስተምር ነበር። በዚያን ጊዜ ነው ጌታ ትንቢቱን ሊፈጽም፣ ትህትናን ሊያስተምር፣ የእዳ ደብዳቤያችንን ሊደመስስ ከገሊላ ተጉዞ በዮሐንስ እጅ ሊጠመቅ ወደ ዮርዳኖስ የወረደው። ምነው ባሪያ ወደጌታው፣ ወታደር ወደንጉስ ይሄዳል እንጅ ጌታ ወደ ባሪያ፣ ንጉስ ወደ ወታደር እንዴት ይሄዳል ቢሉ ስለ ትህትና ነው። ጌታ ወደዚህ ዓለም የመጣው ስለ ትህትና ነው እንጅ ስለ ልዕልና አይደለም። እንዲሁም አብነት ለመሆን ነው። ጌታ ዮሐንስን መጥተህ አጥምቀኝ ብሎት ቢሆን ዛሬ ነገስታት መኳንንት መጥታችሁ አጥምቁን ባሉ ነበር። ወደ ቤተክርስቲያን ወደ ካህናት ሄዶ መጠመቅ እንደሚገባ ሲያስረዳ ነው። በዮርዳኖስ መጠመቁ ትንቢቱ ይፈጸም ዘንድ ነው። መዝሙረኛው ቅዱስ ዳዊት በመዝሙር 114፥4 ላይ
| |||||||||
No comments:
Post a Comment