የሃይማኖትን ጉዞ በማስፈረራራት ማስቆም አይቻልም !!!ዘመኑ ሃሰት የነገሠበት ዲያቢሎስ የሰለጠነበት ሁኗል :: እውነተኛ ክርስቲያኖች ሊሳደዱ ሊገፉ አግልግሎታቸው ሊደናቀፍ የሌለባቸው ክፉ ስም ሊሰጣቸው ይችል ይሆናል፤ ይህን ደግሞ ጌታችን “ ስለ ስሜ በአህዛብ ሁሉ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ “ ማቴ ፳፬፥፱
በማለት እንደተናገረ በጎ እያደረግን ስለስሙ ስንነቀፍ ስንሳደድ ስንጠላ ደስ ሊለን ይገባል :: የተጠራነው ለዚህ ስለሆነ ጥርጥር በሌለበት ሃይማኖት ልንጸናም ያስፈልጋል ::
ቅዱስ ያዕቆብ “ የእምነታችሁ መፈተን ትዕግሥትን እንዲያደርግላችሁ አውቃችሁ ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደሙሉ ደስታ ቁጠሩት :: ” ያዕ ፩፥፪ እንዳለ ስለ እግዚአብሔር ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ብንፈተን ዋጋ ያለው መሆኑን እንወቅ ::ፈተና ፦በእውነት እግዚአብሔርን እያገለገልን ከመጣ የምንደሰትበት እንጅ የምናዝንበት አለመሆኑን የእውነት ተጻራሪ ለሆኑ ሁሉ ማሳየት ተገቢ ነው :: ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ብንነቀፍ ከኛ ጋር ያለው እግዚአብሔር ከሁሉም በላይ ነውና አንሸበርም :: እግዚአብሔርን ሊያሸንፍ የሚችል ማንም የለምና :: “ከእግዚአብሔር ጋር የሚጣሉ ይደቅቃሉ::” ፩ኛ ሳሙ ፪፥፲ ሥራውንም ማስተጓጎል አይቻልም ደግሜ እላለሁ ፡ በእውነት የሃይማኖትን ጉዞ በማስፈረራራት ማስቆም አይቻልም !!!
ቅዱስ ያዕቆብ “ የእምነታችሁ መፈተን ትዕግሥትን እንዲያደርግላችሁ አውቃችሁ ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደሙሉ ደስታ ቁጠሩት :: ” ያዕ ፩፥፪ እንዳለ ስለ እግዚአብሔር ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ብንፈተን ዋጋ ያለው መሆኑን እንወቅ ::ፈተና ፦በእውነት እግዚአብሔርን እያገለገልን ከመጣ የምንደሰትበት እንጅ የምናዝንበት አለመሆኑን የእውነት ተጻራሪ ለሆኑ ሁሉ ማሳየት ተገቢ ነው :: ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ብንነቀፍ ከኛ ጋር ያለው እግዚአብሔር ከሁሉም በላይ ነውና አንሸበርም :: እግዚአብሔርን ሊያሸንፍ የሚችል ማንም የለምና :: “ከእግዚአብሔር ጋር የሚጣሉ ይደቅቃሉ::” ፩ኛ ሳሙ ፪፥፲ ሥራውንም ማስተጓጎል አይቻልም ደግሜ እላለሁ ፡ በእውነት የሃይማኖትን ጉዞ በማስፈረራራት ማስቆም አይቻልም !!!
No comments:
Post a Comment