ሁለት የተለያየ ባህርይ ያላቸው ጓደኛሞች ነበሩ ይባላል አንዱ የነቃ እና ፈጣን ሲሆን ሌላኛው ግን ፈሪ ከመሆኑም በላይ አስተዋይነት የጎደለው ነበር። መንገድ ሲሄዱ ይመሽባቸውና ማደሪያ ባለማግኘታቸው አጥር ተጠግተው ይተኛሉ ቆይቶም አንድ ድምጽ ያነቃቸዋል በዚህ ጊዜ ያ ፈጣንና ንቅ የሆነው ሰው ያንን ድምጽ እየሰማ መተኛት አልቻለም ስለዚህ ነቃ ብሎ ማጣራት ፈለገ። ነገር ግን ያ ድምጽ ከሱ ይልቅ ለጓደኛው የቀረበ መሆኑን ስለአረጋገጠ ሊቀሰቅሰው አሰበ ጓደኛው ግን ምንም እንዳልሰማ ድምፁን አጥፍቶ ተኝቶ ነበር በዚህ ተገርሞ ይቀሰቅሰውና ይህ የምሰማው ድምፅ ምንድነው? ለመሆኑ ይሰማሃል? ይለዋል እሱም መልሶ አዎ ይሰማኛል ዝም ብለህ ተኛ ይለዋል። ጓደኛውም በመገረም ታዲያ እንዴት ዝም ብለህ ተኛህ? ለመሆኑ የምን ድምፅ ነው? ይለዋል በዚህ ጊዜ ቆጣ ብሎ ጅቡ የኔን እግር እየበላ ነው ድምጽ አታሰማ ዝም ብለህ ተኛ አለው ይባላል:: ይህ ሞኝ ሰው አያ ጅቦ እግር በልቶ ሲጨርስ ወደ ጭንቅላት እንደሚመጣ ማሰብ አልቻለም:: ዛሬ የቤተ ክርስቲያን ፈርጥ ጌጥ የካህናት አክሊል የሆኑ ምእመናንን ሰውነት የቆራረጠ ሰይፍ ነገ ዛሬ ዝምታን የመረጡ የቤተክርስቲያን መሪዎችን የሚምር ቢሆን መልካም ነበር ነገር ግን የሰይፍ ባህርይው መቁረጥ መቆራረጥ ነው ይህ ጽዋ እኛ ዘንድ ሳይመጣ ልንነቃ ያስፈልጋል:: ስለዚህ መቆሚያችን ምርኩዛችን ድጋፋችን ምእመናን በሚዘገንን ሁናቴ እየተገደሉ ዝምታን መምረጥ ለመኖር እግር አያስፈልገኝም እንደማለት ነው::
No comments:
Post a Comment