Monday, February 18, 2019

ነነዌን እናስብ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ከሌሎች ልዩ የሚያደርጋት በጎ ሥራዎችንና መልካም ያደረጉ ሰዎችን አክብራ ለትውልድ እንዲተላለፍ ማድረጓ ነው። መቼም በጎ ነገር ሲታወስ ክፋቱም አይረሳምና ለትምህርት እንዲሆን ይዘከራል። ስለ ቃየን ባንሰማ ኖሮ የአቤልን ደግነት ልንረዳው አንችልም ነበርና።

የነነዌ ሰዎችን ስናስብ የእግዚአብሔርን ቸርነትና ከሃሊነት፣ የዮናስን አለመታዘዝ፣ የኃጢአታቸውን መጠን፣ እንዲሁም ለንስሃ ታዛዥነታቸውን እናገኛለን።

እግዚአብሔር ቸርና መኃሪ አምላክ መሆኑን ከቅዱሳት መጻህፍት ተረድተን በህይዎታችን አውቀነዋል። እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ ‘’እርሱ ግን መሓሪ ነው፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር አላቸው፥ አላጠፋቸውምም፤ ቍጣውንም መመለስ አበዛ፥ መዓቱንም ሁሉ አላቃጠለም’’ መዝ 78፥38 እዚህ ላይ ልንገነዘበው የሚገባው የእግዚአብሔር ቸርነት ወደ ንስሃ የሚያቀርብ እንጅ የሰውን ልጅ ነጻነት የሚከለክል እንዳልሆነ ማስተዋል ያስፈልጋል።

Sunday, February 10, 2019


ዘርፌ የተዋህዶ ዘማሪ አልነበረችም።

ዘመኑ የፈጠረው ክፉ ነገር ቢኖር አንድ ሰው እራሱን የፈለገው ቦታ አስቀምጦ በሚዲያ ሲያሰራጭ የጉዳዩን እውነተኛ ነት ሳያረጋግጡ የሚያራግቡ ሰዎች መብዛታቸው ነው። ብዙ ሰዎች ቤተክርስቲያንን ወክለው መግለጫ ይሰጣሉ ብዙ ተቀባይ አላቸው። አንዳንዶች እራሳቸውን ከመንግስት በላይ አድርገው ስለሀገር ጉዳይ መግለጫ ይሰጣሉ እነሱም ብዙ ደጋፊ አላቸው። ይህ ችግር በብዙዎች እይታ ስልጣኔ ተነፍጎ ለኖረ ህዝብ ከአቅሙ በላይ የሚሰጥ ነጻነት የሚያመጣው በሽታ እንደሆነ ታምኖበታል።