እግዚአብሔር ፍጥረታትን ሲፈጥር ያለ ዓላማ የፈጠረው ፍጥረት እንደ ሌለ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል። የፍጥረት ዓይነቱ ልዩ ልዩ እንደሆነው ሁሉ የተፈጠረለት ዓላማውም ልዩ ልዩ ነው። በተለይ የሰው ልጅ ከፍጥረታት ሁሉ ይለያል። ፍጥረታት በሙሉ የራሳቸውን መልክ ይዘው ሲፈጠሩ ሰው ግን እግዚአብሔርን መስሎ ነው የተፈጠረው። ይህም በመሆኑ ዘላለማዊነትና ገዥነት ተሰጥተውት ነበር። በዚህ ክብርና ልዕልና ጸንቶ የቆየው ግን ለሰባት ዓመታት ብቻ ነበር። በጥንተ ጠላቱ ዲያቢሎስ ተታሎ ከአስተዳዳሪነት ወደ ባርነት ከዘላለማዊነት ወደ ኃላፊነት ከገነት ወደ ምድረ ፋይድ ከተሸጋገረ በኋላ ይገዛቸው ያስተዳድራቸው ዘንድ ሙሉ ስልጣን ሰጥቶት የነበረው እንስሳት እንኳን ሸሹት። ለፈጣሪው ያልታመነ ለኛ የሚራራ ልብ እንዴት ይኖረዋል ያሉ ይመስላል።
Wednesday, February 26, 2014
መጠራታችሁን ተመልከቱ
እግዚአብሔር ፍጥረታትን ሲፈጥር ያለ ዓላማ የፈጠረው ፍጥረት እንደ ሌለ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል። የፍጥረት ዓይነቱ ልዩ ልዩ እንደሆነው ሁሉ የተፈጠረለት ዓላማውም ልዩ ልዩ ነው። በተለይ የሰው ልጅ ከፍጥረታት ሁሉ ይለያል። ፍጥረታት በሙሉ የራሳቸውን መልክ ይዘው ሲፈጠሩ ሰው ግን እግዚአብሔርን መስሎ ነው የተፈጠረው። ይህም በመሆኑ ዘላለማዊነትና ገዥነት ተሰጥተውት ነበር። በዚህ ክብርና ልዕልና ጸንቶ የቆየው ግን ለሰባት ዓመታት ብቻ ነበር። በጥንተ ጠላቱ ዲያቢሎስ ተታሎ ከአስተዳዳሪነት ወደ ባርነት ከዘላለማዊነት ወደ ኃላፊነት ከገነት ወደ ምድረ ፋይድ ከተሸጋገረ በኋላ ይገዛቸው ያስተዳድራቸው ዘንድ ሙሉ ስልጣን ሰጥቶት የነበረው እንስሳት እንኳን ሸሹት። ለፈጣሪው ያልታመነ ለኛ የሚራራ ልብ እንዴት ይኖረዋል ያሉ ይመስላል።
Monday, February 24, 2014
በሁሉ አመስግኑ
በአንድ ወቅት አንድ መልካም ሰው ወንጀል ሰርተሃል ተብሎ ፍርድ ቤት ቀረበ አሉ፤ ታዲያ ይህ ሰው ወንጀሉን የፈጸመው ሆን ብሎ ሳይሆን።በአጋጣሚ ነበር፥ ፍርድ ቤት ቀርቦ ዳኛው የምስክሮች ቃል ከሰሙና የቀረበላቸውን ማስረጃ ከመረመሩ በኋላ በሞት እንዲቀጣ ወሰኑበት። በዚህ ጊዜ በፊቱ ላይ ምንም የመረበሽ ስሜት አልታየበትም ነበር። በሁኔታው የተገረሙት ዳኛውና በዙሪያው ያሉት ሰዎች የመጨረሻ የመሰናበቻ ቃሉን ይጠብቁ ጀመር። እግዚአብሔር ይስጥልኝ ክቡር ዳኛ፣ እድሜ ይስጥልኝ፣ ፍርድ የሚሰጥ ዳኛ አያሳጣን ወ ዘ ተ እያለ ምስጋናውን ያወርደው ጀመር አግራሞታቸው የጨመረው ዳኛ ግራ ተጋብተው ,, የፍርዱን ውሳኔ የተረዳው አይመስለኝም በሞት እንዲቀጣ ነው የተወሰነበት ምናልባት ውሳኔውን በደንብ ካልሰማ አስረዱት,, አሉ ። ሰውየውም መለሰ ,, ውሳኔውን በደንብ ተረድቻለሁ ፍርዱም ገብቶኛል የመረዳትም ችግር የለብኝም,, ብሎ መለሰ፤ የዳኛው ጥያቄ ቀጠለ ,, ታዲያ እንዴት ነው የሞት ፍርድ እየተፈረደብህ ፍርድ ቤቱን የምታመሰግነው? አሉ ። ,, ጌታየ ከዚህም የከፋ ፍርድ እኮ አለ መቶ ጅራፍ ተገርፎ ይሙት ቢሉስ ይችሉ አልነበር? ብሎ መለሰ ይባላል።
Friday, February 14, 2014
እስከ መቼ?
ለሰው ልጆች ከእግዚአብሔር ከተሰጡት ስጦታዎች ትልቁ ሃይማኖት ነው። ሰው ከፍጥረታት ሁሉ የላቀ ክብር እንዳለውም የታወቀው በሃይማኖት ኖሮ ከፈጣሪው ጋር ስለሚገናኝ ነው። ታዲያ ይህን ትልቅ ጸጋ አክብሮና ጠብቆ የመኖር ኃላፊነት አለበት። ቅዱሳን እራሳቸውን ለእግዚአብሔር በማስገዛታቸው በዚህ መንገድ ተጉዘው ወደ ዘለዓለም እረፍት እንዲገቡ እግዚአብሔር ሃይማኖትን ሰጥቷቸዋል። ለዚህም ነው ሐዋርያው ቅዱስ ይሁዳ << ወዳጆች ሆይ፥ ስለምንካፈለው ስለ መዳናችን ልጽፍላችሁ እጅግ ተግቼ ሳለሁ፥ ለቅዱሳን አንድ
ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ ይሁዳ 1፥3 >> ያለው። የሰው ልጆች በጸጋ የእግዚአብሔር ልጅነትን ስላገኙ በሃይማኖት ኖረው ያባታቸውን የእግዚአብሔርን ርስት እንዲወርሱ የእግዚአብሔር ፈቃዱ ነው።

Thursday, February 13, 2014
ከጽኑ ቍጣውም ይመለስ እንደ ሆነ ማን ያውቃል?

Subscribe to:
Posts (Atom)