Tuesday, December 31, 2013

ማን ተለወጠ?

የዘመናትን መለዋወጥ ስናነሳ ባለጊዜዎችን ማውሳታችን አይቀሬ ነው። እስቲ ሁላችንም አንድ ነግር እራሳችንን እንጠይቅ, ዘመን  የሚሄደው ወደ ፊት ነው ወደ ኋላ? መልሱ ሊሆን የሚችለው ወደ ፊት ነው። የሚገርመው ነገር ግን ዘመን ወደ ፊት ሲሄድ ባለ ዘመኖች ወደ ኋላ መሄዳቸው ነው።

Friday, December 27, 2013

ከሰው ስለቆጠርከኝ አመሰግንሃለሁ

አንድ ጊዜ የጣለው ሰው በአንድ ሃገር ይኖር ነበር ይባላል። ይህ ሰው ቀድሞ ብዙ ሃብትና ንብረት የነበረው ፣ በሰዎች ዘንድ የተከበረ፣ ባለው ሃብትና ንብረት የተነሳ ብዙዎች የሚወዱት ሰው ነበር። የዚህ ዓለም ሃብት ሲመጣም ድንገት ሲሄድም ድንገት ነውና ሰውየውም ብልሃትና ጥበብ የጎደለው ሰው ስለነበር ሃብቱ እያለቀ መጣ። በዚያው ልክ የወዳጆቹም ፍቅር እየቀዘቀዘ መሄድ ጀመረ። ዓለም ቁልቁለት ላይ ካገኘችን ርህራሄ የላትምና ባጭር ጊዜ ውስጥ ያለው ሃብቱ ሁሉ አለቀ። በቤቱ ውስጥ የነበረውን ንብረት በሙሉ እያወጣ ሸጦ ጨረሰው። በጎረቤቶቹ ዘንድ ቀድሞ የነበረው ታሪክ ተቀይሮ የተጠላና የተናቀ ሆነ። ከሃብቱ ከንብረቱ ይልቅ በሰው ዘንድ መናቁ እጅጉን አሳዘነው። ቀድሞ ከቤቱ ሲወጣ ከበሩ ላይ ተኮልኩለው ከእጁ ምጽዋት የሚጠባበቁ ነዳያን ሳይቀር ይዘባበቱበት ጀመር።

Wednesday, September 18, 2013

የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው ምሳ 10፥7

ያለንበት ዘመን በጎ ነገር የማይፈልቅበት እንዲሁም ቀድሞ የነበረው መልካም ነገር እንደ ኋላቀርነት የሚቆጠርበት ጊዜ ከመሆኑ አንጻር በጥቂቱም ቢሆን በበጎ ሃሳብ ተነሳስቶ ለበጎ ዓላማ በህብረት ለመቆም መጣር በራሱ መስዋዕትነት ነው።

Saturday, May 4, 2013


     እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ ///////

Friday, March 29, 2013

ዲያብሎስን ተቃወሙት ከናንተም ይሸሻል ያዕ 4፥7


ይህ ወቅት በቤተክርስቲያናችን በዓለም ውስጥ ላሉ ሁሉ ፍጥረታት ሰላምና ፍቅርን በረከትን እንዲያገኙ ወደ ፈጣሪያችን በጾም በጸሎት ተወስነን ልመና የምናቀርብበት ጊዜ ነው። ታዲያ በዚህ ጊዜ የሰው ልጅ ሁሉ ጠላት የሆነው ሰይጣን ዲያብሎስ በተለያየ መንገድ ከዓላማችን ወደ ኋላ እንድንል የማይቀይሰው መንገድ አይኖርም። ስለዚህ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በመልእክቱ መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ ኤፌ 6፥12 ” እንዳለው በክርስትና ህይዎት ስንኖር ብዙ ልዩ ልዩ ዓይነት ፈተና ሊገጥመን ይችላል። ይህን ፈተና የምናልፍበት ጥበብና ማስተዋል ከሌለን ጠልፎ ሊያስቀረን ይችላል።