Friday, June 29, 2012

ኮሶ አረህ


ይህ ቦታና አካባቢ ለአዲስ አበባ ቅርብ ቢሆንም ከመልክአምድራዊ አቀማመጡ ገደላማነት የተነሳ ምንም አይነት የዓለም ስልጣኔ ሊደርስበት አልቻለም። ነገር ግን አስቀድሞ የተዘረጋው ሃይማኖታዊና ባህላዊ ስርዓቱ እጅግ ሰልጥነናል ከሚሉት አካባቢዎች የተሻለ ነው። ለምሳሌ በአካባቢው አንድ ጸጉረ ልውጥ ሰው ቢታይ ሁሉም ህብረተሰብ በአይነ ቁራኛ ስለሚከታተለው ምንነቱ በቅጽበት ይታወቃል። በዚህ የተነሳ እስከ አሁን ድረስ በአካባቢው ከኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ውጭ አንድም የእምነት ተቋም አይገኝም። አንድ የሌላ እምነት ሰው በተለያየ ምክንያት ወደ አካባቢው ቢመጣ ከተወሰኑ ቀናት ውጭ እንዲኖር አይፈቀድለትም። መቆየት ከፈለገ ስርዓተእምነቱን ተምሮ እምነቱን ተቀብሎ የመኖር ግዴታ አለበት። ካልፈለገ አይገደድም በሰላም ወደመጣበት የሚገባውን አሸኛኘት ይድረግለታል።

Thursday, June 28, 2012

ምን እያለምን ነው?

በተለያዩ ዘመናት ራእይ አልባ ትውልዶች እንደነበሩ ቅዱስ መጽሐፍ ይነግረናል። ራእይ አልባ የሚባሉት ነገን አስበው ዛሬ መልካም ነገር ለማድረግ የማይተጉ። ወይንም ደግሞ ከዛሬ የተሻለ ነገን ተስፋ አድርገው በመኖር በመከራ የማይታገሱ ናቸው። ለምሳሌ በሎጥ ዘመን የነበሩትን ትውልዶች ብንመለከት በሰዶም ከተማ ያሉ በሙሉ ከሊቅ እስከደቂቅ በኃጢአት የተጨማለቁ ነበሩ። በመሆኑም ለነገ የሚተርፍ አንዳችም መልካም ስራ የሰሩት ስለሌለ ፍጻሜያቸው ጥፋት ሆነ። ለጊዜው እነሱን አነሳን እንጅ ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን ከነሱ በፊትም ሆነ በኋላ በተለያየ ጊዜ ከህገ እግዚአብሔር ፈቀቅ ብለው በኃጢአታቸው ምክንያት አምላካቸውን ያስቆጡ ህዝቦች እንደነበሩ እንረዳለን። ዘፍ 6፥1  ዘፍ 11፥1  1ኛ ሳሙ 2፥31