Saturday, July 2, 2011

የባርነታችሁን ቀንበር ሰብሬያለሁ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን

 ባሪያዎች እዳትሆኑአቸው ከግብፅ ምድር ያወጣኋችሁ እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝ የባርነታችሁን ቀንበር ሰብሬአለሁ ቀና ብላችሁ እንድትሄዱ አድርጌአችኋለሁ። ዘሌ 26፥13

ይህንን ቃል የተናገረው እግዚአብሔር አምላካችን በባሪያው በሊቀ ነቢያት ሙሴ አማካኝነት ነው እስራኤላውያን በግብጽ ባርነት ለ400 ዓመት ከቆዩ በኋላ መከራው ስለጸናባቸው ወደ እግዚአብሔር ጮሁ እግዚአብሔርም ጩኸታቸውን ሰምቶ በሊቀ ነቢያት ሙሴ አማካኝነት ታላላቅ ተአምራትን አድርጎ ከግብጽ ምድር አወጣቸው በግብጽ በረሃ ከዓለት ላይ ውሃ እያፈለቀ ከደመና መና እያወረደ እየመገበ ወደ ተስፋይቱ ምድር  ጉዞ ጀምረው ነበረ ይሁን እንጅ ህዝበ እስራኤል እግዚአብሔር ያደረገላቸውን ውለታ በመዘንጋት ወደ ጣኦት አምልኮ ፊታቸውን በማዞራቸው እግዚአብሔር ተቆጥቷቸዋል

No comments:

Post a Comment