Tuesday, April 4, 2023

ሆሳእና በአርያም

«ሆሳዕና፤ በጌታ ስም የሚመጣ የእስራኤል ንጉሥ የተባረከ ነው፡፡»
ዮሐ.12፥13
 
የአቢይ ጾም ስምንተኛው ሰንበት ሆሳዕና በመባል ይታወቃል፡፡ ሆሳእና የተባለበት ምክንያት በዚህ ሰንበትና በዋዜማዎቹ ዕለታት የሚዘመረው ጾመ ድጓ “ሆሳዕና በአርያም” የሆሳዕናን ቃል በእየቦታው እየጠቀሰና እያነሣ ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እየተመሰገነና እየተዘመረለት በአህያ ውርንጭላ ተቀምጦ ኢሩሳሌም የገባበትን ሁኔታ እየተረከ ስለሚዘምር ይህ ሰንበት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጌትነትና በክብር በውዳሴና ቅዳሴ ሆሳዕና በአርያም እየተባለ በሽግሌዎችና በሕፃናት አንደበት በድንጋዮች ልሣን ሳይቀር እየተመሰገነ ኢየሩሳሌም በአህያ ተቀምጦ ለመግባቱ መታሰቢያ ሆኖ ስለተሰጠ ነው፡፡  ማቴ 21፡1-17፣ ማር 11፡1-10፣ ሉቃ19፡29-38፣ ዮሐ12፡12-15፣ ዘካ 9፤9፣ 2ነገ 9፡13፣ መዝ 117፡25-26፣ ኢሳ 56፡7፣ ኤር 7፡12 እና መዝ 8፡2