Sunday, March 17, 2019

እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ ይሁዳ 1፥3

ባለንበት ዘመን ከራስ አልፎ ስለሰው ማሰብ እጅግ ከባድ እንደሆነ እለት እለት ስለ ሌሎች የሚደክሙ ወገኖች ቢናገሩ መልካም ይሆናል። ነገር ግን ከራስ አልፎ ለሌላው የሚተርፍ ቅንጣትም እንኳ ብትሆን ዋጋ አላት ብየ አምናለሁ። ምናልባት የሁላችንም የእውቀት ደረጃ እና የአስተሳሰብ ችሎታ ስለሚለያይ ለሁሉ መልካም የማይመስል ሃሳብ ልንሰነዝር እንችል ይሆናል ቢሆንም ግን ለተጠቀመበት ሰው በጎ ያልሆነውም ነገር ቢሆን አስተማሪ ነው። 

Wednesday, March 6, 2019

የድሃዋ እንባ መዘዝ

ህዝበ እስራኤል በግብጽ ስደት በነበሩበት ዘመን የደረሰባቸው መከራ እጅግ የከፋ እንደነበር በኦሪት ዘጸአት ምእራፍ 1፥8 ጀምሮ ያለውን ታሪክ ስናነብ በሰፊው እንረዳለን። ምንም እንኳን በስደት በሰው ሀገር የሚኖሩ ቢሆንም እንደሰው ሊሰጣቸው የሚገባውን ክብር በማጣታቸው የመከራ ኑሮ ይኖሩ ነበር። ሰው በሰውነቱ የትም ቢሆን ክብር ሊሰጠዉ ይገባል። ወደ ታሪኩ ስንመለስ እንደ ሰው ሰርቶ መብላት፣ ቀን ሰርቶ ሌሊት ማረፍ፣ ወልዶ መሳም፣ ሰርቶ የድካምን ዋጋ ማግኘትወ ዘ ተ አይፈቀድላቸውም ነበር። ዛሬ በእኛም ሀገር ይህ ሲፈጸም በተደጋጋሚ አይተናል። በእስራኤላውያን ላይ ይህ ግፍ ሊደርስ የቻለው አስቀድሞ ለምድረ ግብጽ መልካም ያደረገ እስራኤላዊ ዮሴፍን የማያውቅ ንጉስ በመነሳቱ ነበር። ክፉና ጠማማ ሰው ደግነትን ቢያውቃትም የበጎ ነገር ጠላት መሆኑ የተለመደ ነው። ዛሬ በየክፍለ ሀገሩ ሰዎች እየተፈናቀሉ ያለው በጎው ነገር ጠፍቶ ሳይሆን የበጎውን ዘመን ሰዎች ታሪክ መዘከር ስለማይፈለግ ነው። እስራኤላውያን ችግራቸውን የሚመለከት ዳኛ በማጣታቸው አምርረው አለቀሱ። የለቅሷቸው መጠን ምን ያክል እንደሆነ ለመረዳት በፈርኦን ላይ የመጣውን መአት አይቶ መረዳት ይቻላል። ዛሬም በሞኝነት አይናችሁ ታውሮ የድሆችን እንባ ቸል የምትሉ ነገ ጎርፍ ሆኖ እናንተንና የኔ የምትሉትን ያሰጥማችኋልና አስቡበት።