Sunday, March 17, 2019
Wednesday, March 6, 2019
የድሃዋ እንባ መዘዝ
ህዝበ እስራኤል በግብጽ ስደት በነበሩበት ዘመን የደረሰባቸው መከራ እጅግ የከፋ እንደነበር በኦሪት ዘጸአት ምእራፍ 1፥8 ጀምሮ ያለውን ታሪክ ስናነብ በሰፊው እንረዳለን። ምንም እንኳን በስደት በሰው ሀገር የሚኖሩ ቢሆንም እንደሰው ሊሰጣቸው የሚገባውን ክብር በማጣታቸው የመከራ ኑሮ ይኖሩ ነበር። ሰው በሰውነቱ የትም ቢሆን ክብር ሊሰጠዉ ይገባል። ወደ ታሪኩ ስንመለስ እንደ ሰው ሰርቶ መብላት፣ ቀን ሰርቶ ሌሊት ማረፍ፣ ወልዶ መሳም፣ ሰርቶ የድካምን ዋጋ ማግኘትወ ዘ ተ አይፈቀድላቸውም ነበር። ዛሬ በእኛም ሀገር ይህ ሲፈጸም በተደጋጋሚ አይተናል። በእስራኤላውያን ላይ ይህ ግፍ ሊደርስ የቻለው አስቀድሞ ለምድረ ግብጽ መልካም ያደረገ እስራኤላዊ ዮሴፍን የማያውቅ ንጉስ በመነሳቱ ነበር። ክፉና ጠማማ ሰው ደግነትን ቢያውቃትም የበጎ ነገር ጠላት መሆኑ የተለመደ ነው። ዛሬ በየክፍለ ሀገሩ ሰዎች እየተፈናቀሉ ያለው በጎው ነገር ጠፍቶ ሳይሆን የበጎውን ዘመን ሰዎች ታሪክ መዘከር ስለማይፈለግ ነው። እስራኤላውያን ችግራቸውን የሚመለከት ዳኛ በማጣታቸው አምርረው አለቀሱ። የለቅሷቸው መጠን ምን ያክል እንደሆነ ለመረዳት በፈርኦን ላይ የመጣውን መአት አይቶ መረዳት ይቻላል። ዛሬም በሞኝነት አይናችሁ ታውሮ የድሆችን እንባ ቸል የምትሉ ነገ ጎርፍ ሆኖ እናንተንና የኔ የምትሉትን ያሰጥማችኋልና አስቡበት።
Subscribe to:
Posts (Atom)