Wednesday, September 12, 2018

ሰውና ማንነቱ

ሰው መሆን ከምንም በላይ ክብር የሚገባው ልዩ ማንነት ነው። ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን ምድራዊ ህይዎታችን ጊዜያዊ ነው። ይህም በመሆኑ በምድር ያለው ሁሉ ኃላፊ ነው። ( ድንኳን የሚሆነው ምድራዊ መኖሪያችን ቢፈርስ፥ በሰማይ ያለ በእጅ ያልተሠራ የዘላለም ቤት የሚሆን ከእግዚአብሔር የተሠራ ሕንጻ እንዳለን እናውቃለንና። በዚህ ውስጥ በእውነት እንቃትታለንና፥ ከሰማይም የሚሆነውን መኖሪያችንን እንድንለብስ እንናፍቃለንና 2ኛ ቆሮ 5፥1)  በቋንቋው የሚመካ ካለ ሞኝ ነው። በዓለም ላይ እንግሊዝኛ የሚናገሩ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ህዝቦች አሉ ማንነታቸው ግን አይደለም። እምነቱን መሰረት አድርጎ ሌላውን በመግፋት የግል ማንነት እንዲኖረው የሚፈልግ ካለ መንፈሱና ሥጋው የተጣሉበት ማስተዋል የተነሳው መሆን አለበት። አንተ የምታምነው አምላክ የሁሉ ፈጣሪ እንጅ የአንተ የግል ንብረት አይደለም። የትውልድ አካባቢውን መሰረት በማድረግ የነገሌ ዘር ነኝ ብሎ እራሱ ከሌላው ለመለየት አጥር የሚያጥር ካለ በዓለም ውስጥ የተሸነፈ ሰው ነው። ይህ ውሳኔ የሰው ሳይሆን የእግዚአብሔር ነው። ማንም በራሱ ላይ አንዳች ማድረግ የሚችል የለም። ጌታ በወንጌል እንዲህ ብሎ እንደተናገረው   ( ከእናንተ ተጨንቆ በቁመቱ ላይ አንድ ክንድ መጨመር የሚችል ማን ነው? ማቴ 6፥27)