ስለ ዘመናችን የስልጣኔ ደረጃ ስናነሳ ሁላችንም የምንገነዘበው ነገር አለ። ኃያላን መንግሥታት ቀድሞ ከነበራቸው አመለካከት ይልቅ የአሁኑ የተሻለ በመሆኑ የስልጣኔ መሪዎች ይባላሉ። ቀድሞ በኃይል ሁሉን ማሸነፍ የሚችሉ ይመስላቸው ስለነበር የሌሎችን መብት በመግፈፍ በጭቆና ይገዙ ነበር። ዛሬ ላይ ያንን አመለካከት ከመጥላታቸውም በላይ በየጊዜው ሲያወግዙ እንሰማቸዋለን። ምድራዊ ገዥዎች ምንጊዜም ከስህተት የማይርቁ ቢሆኑም የሰውን ልጅ መብት ለማስከበር በየሀገራቸው የሚጥሩ መሪዎች በመኖራቸው በደልና ስቃይ ጎልቶ እንዳይወጣ ለማድረግ ችለዋል።