Friday, February 3, 2017

የማልወደውን አደርጋለሁ !

 ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ እንዳለ ዮሐ 8፥12 እርሱ ለመረጣቸው ሁሉን ትተው ለተከተሉት ኃዋርያትም እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ ብሏቸዋል ማቴ 5፥14

ዓለም በኃጢዓት ጨለማ ውስጥ ተውጦ ሳለ እውነተኛው ብርሃን መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ ለአዳም የገባውን ቃል በፈጸመ ጊዜ ጨለማው ዓለም ብርሃን ወጥቶለታል። ይህም ሆኖ የሰው ልጆች ከጨለማ ወደ ብርሃን ለመምጣት ሲቸገሩ ታይተዋል። በዚህም ምክንያት። የብርሃኑን መንገድ የሚያሳዩ ኃዋርያትን መርጦ ወደ ዓለም ልኳቸዋል። ማር 16፥15 ዮሐ 17፥18