ከፍጥረታት መካከል ሰውና እንስሳት ከድርጊት ጋር በተያያዘ የሚሰጣቸው ስም አለ። ያ ስም ቀድሞ የተሰጣቸው ሳይሆን በኋላ
ከተፈጥሯዊ ጠባያቸው ወጣ ባለ መንግድ ድርጊትን ሲፈጽሙ በመገኘታቸው ነው። የሰውን ብንመለከት በመልካም ሰዎች የተነሳ ለእግዚአብሔር
ልንሰጠው የሚገባውን የአክብሮት ስያሜ ለሰዎች እንሰጣለን። ለምሳሌ ቸር፣ ሩህሩህ፣ ለጋስ ፤ትሁት፤ቅን ,,,,,,,, ወዘተ በተቃራኒው ደግሞ ለዲያቢሎስ ልንሰጠው የሚገባውን ስያሜ ለሰዎች የምንሰጥበት
ጊዜ አለ ምክንያቱም በግብር ስለሚመስሉት ነው። ለምሳሌ ክፉ፣ ጨካኝ ፣ አረመኔ፣ ነፍሰ ገዳይ፣ አውሬ , , , , , ወዘተ ልንል
እንችላለን።