Saturday, December 29, 2012

የጸናውን አስቡ እብ 12፥3

 
ሰሞኑን በምንሰማው ነገር ብዙዎቻችን ክርስቲያኖች በተለያየ ሃሳብ ውስጥ እንዳለን ይታወቃል። በተለይ የወሬ ገበያው የደራላቸው ሚዲያዎች የቤተክርስቲያንን ጉዳይ የራሳቸው በማስመሰል ብዙዎችን ወደ አልተፈለገ አቅጣጫ እየመሩ እንደሆነ በግልጽ እየታየ ነው። የቤተክርስቲያን ጉዳይ እለት እለት የሚያስጨንቃቸው አካላት እንዳሉት ሁሉ አንድነቷና ሰላሟ ወደነበረበት ቢመለስ የእለት እንጀራቸው የሚያሳስባቸው ጥቂቶች አይደሉም። ምክንያቱም በአባቶች መካከል የተፈጠረው ልዩነት ለወንበዴዎች ሰርግና ምላሽ ሆኖላቸው ነበር። “ ግር ግር ለሌባ ይመቻል አይደል ” የሚባለው ፣ አሁን ስለ ሰላም ከሚጨነቁት አካላት በላይ የነበረው አለመግባባት እንዲቀጥል የሚደክሙት ወገኞች ስራ በዝቶባቸዋል። በጣም የሚደንቀው በሰላም እና በአንድነት እየኖሩ ሁሉን ማግኘት እየተቻለ ለምን ቤተክርስቲያኒቱን በጥብጠው እራሳቸውን እንደሚበጠብጡ ነው የማይገባኝ፥ የሰላም ሰው የፍቅር ሰው መባል በሰውም ሆነ በእግዚአብሔርም ዘንድ ያስከብራል እንጅ ውርደት የለበትም።