በክፍል አንድ ለማየት እንደሞከርነው የሊቀነቢያት ሙሴ ህይዎት ለብዙዎቻችን
የሚያስተምረው በጎ ነገር እንዳለ ለመረዳት እንደቻልን እገምታለሁ። ዛሬም በክፍል ሁለት ከሱ ህይዎት ተነስተን በእኛ ህይዎት ሊኖር
ስለሚገባው ነገር ለማየት እንሞክራለን ስለሁሉም የአምላክ ቸርነት
የወላዲተ አምላክ አማላጅነት ከሁላችን ጋራ ይሁን።
1/ የሙሴ ትህትናቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን ከሰው ወገን እንደ ሊቀነቢያት ሙሴ ያለ ትሁት ሰው አልነበረም << ሙሴም በምድር ላይ ካሉት ሰዎች ሁሉ ይልቅ እጅግ ትሑት ሰው ነበረ። ዘኁል 12፥3